የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በክልሉ ደረጃ ለሚያደርጋቸው የላቁ ተግባራት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች የግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች እውቅና መድረክ ላይ የ 2017 ዓ.ም ልዩ ተሸላሚ በመሆን የእውቅና እና አድናቆት በፕሪሚየም ደረጃ የዋንጫ ተሸላሚ በመሆኑ የላቀ ደስታ ይሰማናል።
ይህ እውቅናና ሽልማት በይበልጥ እጅግ በርትተንና ተቀናጅተን እንድንሰራ የሚያደርገን መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።
በግንባር ቀደምትነታችሁም ለተሸለማችሁ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን።በየዓመቱ ካላችሁበት ደረጃ ወደላቀው እንድትሸጋገሩና እንድትበረቱ እናሳስባለን።
ታህሳስ 2018 ዓ.ም
አርባ ምንጭ









